Ethiopia Today

Ethiopia Today A global news provider! Engineers | Architects I Interior Designers I Builders I 3D Visualizers!
(2)

የጥንቃቄ = መልዕክት  ዛሬ ግንቦት 06/09/2018ዓ/ም በዕለተ ሀሙስ ከቀኑ 8:00 ሰዓት በግምት በምሆንበት ጊዜ ስሙ ሁሴን ወዕሌቦ ሁሎሮ አድራሻው ከንባታ ዞን አድሎ ዙርያ ወረደ ሸሸራ ...
14/05/2026

የጥንቃቄ = መልዕክት

ዛሬ ግንቦት 06/09/2018ዓ/ም በዕለተ ሀሙስ ከቀኑ 8:00 ሰዓት በግምት በምሆንበት ጊዜ ስሙ ሁሴን ወዕሌቦ ሁሎሮ አድራሻው ከንባታ ዞን አድሎ ዙርያ ወረደ ሸሸራ ቸፌ ቀበሌ ነዋሪ የሆነውን ግለሰብ አንድ አርሶ አደር ግለሰብ ስሙ አቶ አበራ የምባል አድራሻው ሀ/ቁ/ከ/በሜጦ ቀበሌ በጋለቶ ቀጠና ነዋሪ ሲሆን ግለሰቡ በሜጦማ ቀበሌ በዋንጃ ዋልድያ በቡሼ ንዑስ መንደር ውስጥ የዘረውን ቦቆሎ ለማስኮተኮት

ከዝህ በላይ በስም የተጠቀሰውን ሟች ሁሴን ወዕሌቦ ሁሎሮ የተባለውን ግለሰብ ቦቆሎውን እንድኮተክትለት በገንዘብ 700ብር ተስማምቶ
ለስራ ያስገባዋል። ይህ ግለሰብ ስራውን የጀመረው ከረፋዱ 4:00 ሰዓት አከባቢ ስሆን ለዝህ ግለሰብ/ሟች/የአቶ አበራ ባለቤት ወደ በቆሎ ማሳ ምሳና ውሃ ይዛለት ትሄዳሌች

ምሳውን ሴትዮዋ ስትወስድለት ሟቹ በኩትኳቶ ስራው ላይ እንደነበር ትናገራሌች ከዝያ ሴትዮዋ ሰራተኛውን ወደ ጥላ ሆነህ ምሳህን ብላ ትለዋሌች ከዝያ ሟቹም እሽ ይልና እዝህ ጋ አምጭልኝ ብሎ በቆርቆሮ ወደታጠረው አጥር ጥግ ሄዶ ቁጭ እንዳላ ምሳውንም ሳይበላ የመጨረሻ ምሳውን የወሰደችለት ሴትዮዋ ምግቡንም ከዛንብሏም ሳታወጣ እዛቹ ተደግፎ የተቀመጠውን የቆርቆሮ አጥሩን እንደተደገፋም በዛችው ቅጽበት ምግቡንም ሳይበላ ህይወቱ ልያልፍ እንደቻላ ትናገራሌች

በወቅቱም የሟችን ሁኔታ የተመለከተችው ሴትዮ ሌሎች ሰዎችን ጠርታ ስለሟቹ አሟሟት ሁኔታ ታስረዳሌች ከዝያ በመቀጠል ለፖሊስ ይደዎላል በፍጥነት የደረሰው ፓሊስም የሟቹን ማንነትና አድራሻ ለማወቅ በአስክሬኑ ላይ መታወቂያ ይፈልግና ልያገኝ አልቻለም ከዝያም ሟቹን ከሰራተኛ ተራ አምጥቶ የቀጠረውን ግለሰብ/አቶ አበራ የተባለውን አስጠርቶ

ይህን ግለሰብ/ሟች/ስሙንና አድራሻውን ጠይቄህ ነበር ወይ? ስል ፓሊስ ይጠይቀዋል ስጠይቀው ስሙን አልጠየኩም አድራሻውን ስጠይቀው አድሎ ዙሪያ ወረዳ ከሸሸራቸፌ እንደመጣ ነግሮኛል መታወቂያ ግን አልጠየኩትም ስል ለፖሊስ ይናገራል።

ከዝያ ሪፖርት የተደረገለት የቁሊቶ ከተማ ፓሊስ አዛዥ ረ/ኢ/ር ሹክራላ ሸ/ሱጋቶ የወንጀል መከላል ፓ/አባላትንና ፓትሮል መኪና ይልካል አስክሬኑ በዝህ መኪና ተጭኖ ምናልባት የምያውቀው ሰው ከተገኘ በምል ወደ ሰራተኛ ተራ ተወስዶ የምያውቀው ሰው ከተገኘ ተብሎ ስጠያያቅ የሟችን ሙሉ ስሙንና አድራሻውን የምያውቅ ሰው ተገኝቷል በዝህ መልኩ ለማወቅ ተችሏል።

ዘመድ የምሆንለትን ሰው በዝህ መልኩ እንድመጣ የተደረጋ ስለሆነ

አሁን ለህብረተሰባችን የምናስተላልፈው ዋናው
መልዕክታችን ማንኛውንም የቀን ሰራተኛ ለስራ ስንፈልግ / ስንቀጥር አስቀድመን ስሙንና ሙሉ አድራሻውን በትክክል የምገልጽ ብቻል የድጅታል መታወቂያ ካልሆነም ብያንስ የቀበሌ መታወቂያ መያዙን ያረጋግጡ።

ሉዊስ ኤንሪኬ፡- “በመልስ ጨዋታ የተለየ ጨዋታ አልጠብቅም። የተቻልንን እንሞክራለን።” 🔥
29/04/2026

ሉዊስ ኤንሪኬ፡- “በመልስ ጨዋታ የተለየ ጨዋታ አልጠብቅም። የተቻልንን እንሞክራለን።” 🔥

የትራንስፖርት ታሪፍ በተወሰነው መሰረት እንዲቀጥል ትዕዛዝ ተላለፈየትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የትራንስፖርት ታሪፍ በተወሰነው መሰረት ብቻ እንዲቀጥል ተዕዛዝ አስተላልፏል።ሚኒስቴሩ ...
29/04/2026

የትራንስፖርት ታሪፍ በተወሰነው መሰረት እንዲቀጥል ትዕዛዝ ተላለፈ

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የትራንስፖርት ታሪፍ በተወሰነው መሰረት ብቻ እንዲቀጥል ተዕዛዝ አስተላልፏል።

ሚኒስቴሩ የትራንስፖርት አገልግሎት ወደ መደበኛ ሁኔታ መመለሱን ለማሳወቅ ባወጣው መግለጫ÷ በመካከለኛው ምሥራቅ የተከሰተው ግጭት በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሮ የነዳጅ ዋጋ ግሽበትና በአቅርቦት ላይ መስተጓጎል እንዲፈጠር አድርጓል ብሏል።

ይህም ሁኔታ በኢትዮጵያ የናፍታ ዕለታዊ አቅርቦትን ከ9 ሚሊየን ሊትር ወደ 4 ነጥብ 5 ሚሊየን ሊትር እንዲቀንስ አድርጎ በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የሚታወቁ መስተጓጎሎችን አስከትሎ እንደነበር አስታውሷል።

መንግሥት ይህንን ችግር በፍጥነት ለመቆጣጠር የታሪፍ ማሻሻያ፣ የአቅርቦት አደረጃጀት ማሻሻል እና የሎጂስቲክስ ቅንጅት ማጠናከርን ጨምሮ በርካታ አስቸኳይ እና ዘላቂ ርምጃዎች መውሰዱን አመልክቷል።

ይህም የውጭ ጫናዎች ቢኖሩም የሀገር ውስጥ ኢኮኖሚ መረጋጋትን በመጠበቅ እና የሕዝብ አገልግሎቶች እንዳይቋረጡ በማድረግ በኩል መንግሥት የሕዝብ ጥቅምን በማስቀደም የሚከተለውን የፖሊሲ አቅጣጫ የሚያሳይ መሆኑን አስረድቷል።

ዛሬ የገንዘብ ሚኒስቴር በይፋ እንዳሳወቀው የነዳጅ አቅርቦት ወደ መደበኛ ሁኔታው ተመልሷል ያለው ሚኒስቴሩ÷ ይህ ሁኔታ በትራንስፖርት ዘርፍ የተፈጠሩ መስተጓጎሎች በፍጥነት እንዲፈቱ ያስችላልም ብሏል።

በመሆኑም ከዛሬ ጀምሮ ቀደም ሲል በነዳጅ እጥረት ምክንያት የተፈጠሩ የትራንስፖርት አገልግሎት መስተጓጎሎች ሙሉ በሙሉ እንዲቀረፉ፣ ከአዲስ አበባ እስከ ክልሎች የሚገኙ ሁሉም የዘርፉ አመራሮች እና ተዋናዮች ታሪፍ በተወሰነው መሰረት ብቻ እንዲቀጥል በጥብቅ እንድከታተሉና ትግበራውንም በጋራ ግብረ ኃይል እንዲያረጋግጡ አሳስቧል፡፡

መንግሥት የሕዝብ ኑሮ መረጋጋትን ማረጋገጥ፣ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ቀጣይነትን መጠበቅ እና የትራንስፖርት አገልግሎት በዘላቂ መልኩ እንዲጠናከር ያለውን ቁርጠኝነት ይቀጥላል ሲልም አስገንዝቧል።

በ'ፊንቴክ ኢንቨስትመንት' የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ አቃቢ ህግ ክስ መስርቶ እንዲያቀርብ ሰባት ቀናት ተፈቀደለት። የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፥ ...
29/04/2026

በ'ፊንቴክ ኢንቨስትመንት' የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ አቃቢ ህግ ክስ መስርቶ እንዲያቀርብ ሰባት ቀናት ተፈቀደለት።

የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፥ በ'ፊንቴክ ኢንቨስትመንት' የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ መርማሪ ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ እንዲያቀርብ ለዛሬ ሚያዚያ21/2018 ዓም ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።

በቀጠሮው መሰረት የተሰየመው ችሎቱ ሚያዝያ 9/2018 ዓም በተሰየመበት ወቅት መርማሪ ፖሊስ ጠይቆት ከነበረው የተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ውስጥ ችሎቱ "ፖሊስ የመጨረሻ የምርመራ መዝገቡን አደራጅቶ እንዲያቀርብ በሚል" በሰጠው የሰባት ቀናት ጊዜ መሰረት በፖሊስ በኩል የተጠናቀረውን የምርመራ መዝገብ በዛሬው ዕለት አድምጧል።

መርማሪ ፖሊስ በተሰጠው ጊዜ የክስ መዘገቡን አደራጅቶ ለአቃቢ ህግ ማቅረቡን ገልጿል።

በአጠቃላይ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ከ 7 ሺ ገጾች በላይ የክስ መዝገብ መደራጀቱን የገለጸው አቃቢ ህግ በመዝገቡ ላይ 1ሺ 400 ተበዳዮች መኖራቸውን ከእነዚህ ተበዳዮችም ፖሊስ የ150ውን ቃል መቀበሉን ፣ ከ 12 ሚዲያዎች፣ከ 15 ባንኮች ደግሞ በተጠርጣሪዎች ዙሪያ ያሉትን መረጃዎችን መሰብሰቡን በዝርዝር አስረድቷል።

ስለሆነም ያለውን የማስረጃ ብዛት፣ የተበዳዮችን ብዛት፣ እና የጉዳዩን ክብደት ከግምት ውስጥ በማስገባት መዝገቡ ሊያስከትል የሚችለው ተደራራቢ ክስ የመመስረቻ የ 10 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠን ሲል አቃቢ ህግ ችሎቱን ጠይቋል።

የተጠርጣሪ ጠበቆች በበኩላቸው "ተጠርጣሪዎቹ ማህበራዊ መሰረት ያላቸው፣ የጤና እክል ያለባቸው እንዲሁም በተፈለጉበት ጊዜ ሊመጡ የሚችሉ መሆናቸውን በመጥቀስ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ተከራክረዋል።

በተጨማሪም የምርመራ መዝገቡ ተጠናቆ ለአቃቢ ህግ መቅረቡን በመግለጽ አቃቢ ህግ ክሱን እስኪመሰርት ደንበኞቻችን በእስር መቆየት የለባቸውም በማለት ለችሎቱ አስረድተዋል።

የግራ ቀኙን ክርክር ያደመጠው ችሎቱ አቃቢ ህግ ለክስ መመስረቻ ከጠየቀው የ 10 ቀናት ጊዜ ውስጥ ሰባቱን ቀናት በመፍቀድ ክስ መስርቶ እንዲያቀርብ ለ28/08/18 ዓ/ም ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል።

 ህወሓት፤ ሌተናንት ጄነራል ታደሰ ወረደ የሥልጣን "ርክክብ" ካላደረጉ "ስህተት ነው የሚሆነው" ሲል ገለጸ።የህወሓት ቃል አቀባይ አቶ ሚካኤል አስገዶም ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ፤ የ...
29/04/2026



ህወሓት፤ ሌተናንት ጄነራል ታደሰ ወረደ የሥልጣን "ርክክብ" ካላደረጉ "ስህተት ነው የሚሆነው" ሲል ገለጸ።

የህወሓት ቃል አቀባይ አቶ ሚካኤል አስገዶም ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናንት ጄነራል ታደሰ ወረደ "ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ርክክብ" የማይፈጽሙ ከሆነ "ስህተት" እንደሚሆን ተናግረዋል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር "እየፈረሰ በመሆኑ" ከፌደራል መንግሥት ጋር ያለው የግንኙነት "ገመድ መበጠሱን" ገልጸዋል።

ከስድስት ዓመት በፊት በክልሉ ምርጫ "የተመረጠው የትግራይ መንግሥት ምክር ቤት ወደ ሥራ እንዲመለስ" መወሰኑን አስታውሰዋል።

" የፕሪቶሪያ ስምምነቱን ያፈረሰው የፌደራል መንግሥት ነው። እኛን ሳያማክር [ሌተናት ጄነራል ታደሰን] ለብቻው ሹሞ የላከልን ፌደራል መንግሥት ነው " ብለዋል።

በ2012 የተደረገው ምርጫ በስምምነቱ መሠረት "ውድቅ" ሳይሆን "ታግዶ" የቆየ መሆኑን ገልጸው፤ " አሁን ባለው ሁኔታ አዲስ ምርጫ ማድረግ ስለማይቻል የቀድሞው ምክር ቤት ወደ ሥራ መመለሱ ሕጋዊ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

ጄነራል ታደሰ በምክር ቤቱ ለሚመረጠው ፕሬዝዳንት ሥልጣን ያስረክባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸው፤ " ከዚህ ውጭ የሚሄድ ሰው ካለ ወይም ከዚህ ውጪ ከሄዱ ግን ስህተት ነው የሚሆነው። ትክክል አይሆንም " ብለዋል።

ምክር ቤቱ ወደ ሥራ ከተመለሰ በኋላ አዲስ አስፈጻሚ ካቢኔ እና ፕሬዝዳንት እንደሚሰይም ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንት ጄነራል ታደሰ ወረደ ከዚህ ቀደም በሰጡት መግለጫ " በጊዚያዊ መንግስት ላይ መፈንቅለ መንግስት (ኩዴታ) ለማድረግ እንዳታስቡት፤ እንዳትተገብሩት " ብለው ነበር።

" ' ነባር መንግስት ይመለስ ' የሚለው የህወሓት ውሳኔ አደገኛና ተጨማሪ ግጭትና ጥፋት የሚጋብዝ ነው። ውሳኔው ከተተገበረ ውድቀት እንጂ ድል አይገኝም " ሲሉ ነው ያስጠነቀቁት።

መረጃው ከቢቢሲ የተወሰደ ሲሆን ቲክቫህ ኢትዮጵያ በአሁኑ አስተያየት ዙሪያ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የሚሰጠውን ምላሽ ተከታትሎ ያቀርባል።

ሚያዚያ 21 ቀን 2018 ዓ/ም

የናፍጣ አቅርቦት ከዛሬ ጀምሮ ቀድሞ ወደ ነበረበት እንዲመለስ መንግሥት ወስኗል - የገንዘብ ሚኒስትር    አሕመድ ሽዴ  *   *   *በኢትዮጵያ የአንድ ቀን የናፍጣ አቅርቦት ከመካከለኛው ም...
29/04/2026

የናፍጣ አቅርቦት ከዛሬ ጀምሮ ቀድሞ ወደ ነበረበት እንዲመለስ መንግሥት ወስኗል - የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ

* * *

በኢትዮጵያ የአንድ ቀን የናፍጣ አቅርቦት ከመካከለኛው ምሥራቅ ግጭት በፊት ወደ ነበረበት 9 ሚሊዮን ሊትር እንዲመለስ መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ ዛሬ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

በመካከለኛው ምሥራቅ ግጭት ምክንያት የዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ መጨመር እና አቅርቦት ላይ መስተጓጎል መፈጠሩ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም በኢትዮጵያ የአንድ ቀን የናፍጣ አቅርቦት ወደ 4.5 ሚሊዮን ሊትር ወርዶ ነበር።

አሁን የአንድ ቀን የናፍጣ አቅርቦት ወደ ቀደመው 9 ሚሊዮን ሊትር እንዲመለስ መወሰኑን ተከትሎ ከዛሬ ጀምሮ ከጅቡቲ ወደ አዲስ አበባ መጓጓዝ እንደሚጀመር የገለጹት የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ ወደ ክልሎች ደግሞ ከነገ ጀምሮ መጓጓዝ ይጀምራል ብለዋል።

እስካሁን የቤንዚን እና የአውሮፕላን ነዳጅ ሙሉ በሙሉ ቀድሞ በነበረው መጠን እየቀረበ መሆኑንም የገንዘብ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተው የነዳጅ አቅርቦት መስተጓጎል ኢኮኖሚው ላይ የሚያደርሰውን ጫና ለመከላከል መንግሥት በልዩ ግዢ በከፍተኛ ዋጋ ነዳጅ ገዝቶ እያቀረበ መሆኑንም ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ አስረድተዋል።

በዚህም ምክንያት በአሁኑ ወቅት መንግሥት በየወሩ ቀድሞ ከነበረው በተጨማሪ 20 ቢሊዮን ብር እየደጎመ ነዳጅ እያቀረበ መሆኑን ነው የገለፁት።

በዓለም ዋንጫው አፍን ሸፍኖ ማውራት ከሜዳ ያሰናብታል**************ዓለም አቀፉ እግር ኳስ ፌደሬሽኖች ማኅበር ይህን ውሳኔ ያሳለፈው በተጫዋቾች ላይ የሚደርስ አግባብ ያልሆነ ትንኮሳን ...
29/04/2026

በዓለም ዋንጫው አፍን ሸፍኖ ማውራት ከሜዳ ያሰናብታል
**************

ዓለም አቀፉ እግር ኳስ ፌደሬሽኖች ማኅበር ይህን ውሳኔ ያሳለፈው በተጫዋቾች ላይ የሚደርስ አግባብ ያልሆነ ትንኮሳን ለመከላከል ነው። በተለይም በቅርቡ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች የታዩ እንቅስቃሴዎችን ዋቢ አድርጓል።

እናም በዓለም ዋንጫው የሚሳተፉ ተጫዋቾች አንሰማም ብለው አፋቸውን በመሸፈን ከባላጋራ ተጫዋቾች ጋር ንግግር ቢያደርጉ በዋና ዳኛው የቀጥታ ቀይ ካርድ ከሜዳ ይሰናበታሉ ተብሏል።

በተጨማሪም የዳኛ ውሳኔን በመቃወም ሜዳ ለቀው የሚወጡ ተጫዋቾችም በዝምታ አይታለፉም፤ እጣቸው ቀይ ካርድ እንደሆነ ተገልጿል።

በእድሪስ አህመድ

በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች እየታየ ያለው የነዳጅ (ናፍጣ) መጥፋት በዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ላይ እያሳደረ ያለው ከፍተኛ ጫና እየባሰበት ነው።በተለይም ነዳጅ አሁንም በህገ-ወጥ መንገድ በው...
28/04/2026

በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች እየታየ ያለው የነዳጅ (ናፍጣ) መጥፋት በዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ላይ እያሳደረ ያለው ከፍተኛ ጫና እየባሰበት ነው።

በተለይም ነዳጅ አሁንም በህገ-ወጥ መንገድ በውድ ዋጋ እየተሸጠ ነው። ነዳጅ እጥረቱ እንዳለ ሆኖ ህገወጥ ንግዱ ግን ጦፏል። ተሰልፈው የሚቀዱ ተሽከርካሪዎች ከጀርባ ሄደው አውርደው በከፍተኛ ዋጋ ይሸጡታል።

የትራንስፖርት እና ሸቀጦች ዋጋም ንሯል።

በአንዳንድ አካባቢዎች 30 ሊትር ናፍጣ እስከ 27 ሺህ ብር እየተሸጠ እንደሚገኝ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ገልጸዋል። ይህ ሁኔታ ቀደም ሲል አጭር ርቀት 150 ብር የነበረውን የትራንስፖርት ታሪፍ ከ500 ብር በላይ እንዲያሻቅብ አድርጓል።

ነጋዴው " ነዳጅና የትራንስፖርት ወጪ ነዳጅ ተወዷል " በሚል ያወጣውን ለማካካስ ዋጋ ሲጨምር ገቢው የማይነቃነቀው የህብረተሰብ ክፍል ፈተናውን እያየ ይገኛል።

በተለይም ቋሚ ገቢ ያለው ደመወዝተኛ ማህበረሰብ የቤት ኪራይን ፣ የምግብ ወጪንና የልጆችን የትምህርት ቤት ክፍያ መሸከም ከብዶት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።

የነዳጅ እጥረትና የጥቁር ገበያ መስፋፋቱ በሰንሰለት ሁሉንም የንግድ ዘርፎች እየነካ ነው።

በተጨማሪ አዲስ አበባ ላይም አሁንም የነዳጅ ችግሩ እንዳለ ሲሆን ናፍጣ ለማግኘት አራት ቀን ድረስ ውጭ ይታደራል። እንደዛም ሆኖ " አለቋል " ሊባል ይችላል።

‎⭕️ የማንቸስተር ዩናይትድ የመጨረሻ 4 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች በኢትዮጵያ ቀን እና ሰዓት አቆጣጠር‎‎❔ በእነዚህ ጨዋታዎች ስንት ነጥብ ያገኛል ❔
28/04/2026

‎⭕️ የማንቸስተር ዩናይትድ የመጨረሻ 4 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች በኢትዮጵያ ቀን እና ሰዓት አቆጣጠር

‎❔ በእነዚህ ጨዋታዎች ስንት ነጥብ ያገኛል ❔

የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ " ሙሉ በሙሉ " ሊፈርስ ነው ?ከሰሞኑን " የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ሙሉ በሙሉ  ሊፈርስ ነው " ሲል ' መሰረት ሚዲያ ' ምንጮችን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።ይህ...
28/04/2026

የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ " ሙሉ በሙሉ " ሊፈርስ ነው ?

ከሰሞኑን " የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ሙሉ በሙሉ ሊፈርስ ነው " ሲል ' መሰረት ሚዲያ ' ምንጮችን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።

ይህን መረጃ ተከትሎ በርካቶች " በተቋሙ ውስጥ ተሰንደው የሚገኙ በርካታ ማስረጃዎቻችን ምን ሊደረጉ ነው ? " ሲሉ ሲጠይቁ ተስተውለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩ ምንድነው ? ሲል የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎትን ማብራሪያ ጠይቋል።

ተቋሙ የቅርንጫፍ ቅነሳ ሊኖር እንደሚችል ጠቁሞ " ሊፈርስ ነው " በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰው መረጃ ግን ፍጹም ሀሰተኛ ነው ሲል ገልጿል።

የፌደራል የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃሚድ ኪኒሶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ማብራሪያ፣ ተቋሙ ከ " መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት " ጋር በቅንጅት መስራት መጀመሩን ገልፀው ፤ ይህም የአሰራር ሽግግር እንጂ የመፍረስ ሂደት እንዳልሆነ ተናግረዋል።

አቶ ሃሚድ " መሶብ ላይ ያሉት ተቋማት አገልግሎቱ የእነሱ ነው ፤ ስራቸውን እየመሩ ይሰራሉ የእኛ መስሪያ ቤትም በነበረበት ሁኔታ ስራውን ይቀጥላል " ብለዋል።

ይሁን እንጂ፣ አገልግሎቱን በአንድ ማዕከል ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ምክንያት " የቅርንጫፎች ቅነሳ አካሄድ ሊኖር ይችላል " ሲሉ ተናግረዋል።

ተቋሙ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ ደግሞ፣ በአሁኑ ወቅት በፌዴራልና በአዲስ አበባ በሚገኙ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች መሶብን ጨምሮ ዲጂታላይዝድ የሆነ አገልግሎት ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ገልጿል።

አገልግሎቱ በቀን ከ6 ሺህ በላይ ተገልጋዮችን በማስተናገድ ላይ እንደሚገኝ የጠቀሰው መግለጫው፣ ተቋሙ " ሊፈርስ ነው " ተብሎ የሚወራው ወሬ ሀሰተኛ መረጃ ነው ብሏል።

ተገልጋዮች በሁሉም ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች የሚፈልጉትን የሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል።

⚽️ ውጤቱን ይገምቱ! የሞባይል ካርድ ይሸለሙ!Man United 🔴 vs ⚪️ Brentford🗓 ሰኞ ሚያዚያ 19 ⏰  ከምሽቱ 04:00 በትክክል የገመቱ ሶስት ተሸላሚዎች እያንዳንዳቸው1ኛ/ 10...
27/04/2026

⚽️ ውጤቱን ይገምቱ! የሞባይል ካርድ ይሸለሙ!
Man United 🔴 vs ⚪️ Brentford
🗓 ሰኞ ሚያዚያ 19 ⏰ ከምሽቱ 04:00
በትክክል የገመቱ ሶስት ተሸላሚዎች እያንዳንዳቸው
1ኛ/ 100
2ኛ/ 50
3ኛ/ 25 ብር ካርድ
ፖስቱን ሼር ምድረግ እንዳይረሳ

Address

Alaba K'ulito

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopia Today posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share