Kaffa Zone Work,Technique , Enterprise & Industry Dev't Dep't

Kaffa Zone  Work,Technique , Enterprise & Industry Dev't Dep't 0473310044

28 የተለያዬ ዓይነት ያላቸው ማሽኖች ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች  ተሰራጩ።ከደቡብ ካፕታል በሊዝ ማሽን የተገኙ 28 መሽኖች ለ6 ኢንተርፕራይዞች ተሰራጭተዋል።ማሽኖቹ  የተለያዬ ግል...
04/12/2023

28 የተለያዬ ዓይነት ያላቸው ማሽኖች ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ተሰራጩ።
ከደቡብ ካፕታል በሊዝ ማሽን የተገኙ 28 መሽኖች ለ6 ኢንተርፕራይዞች ተሰራጭተዋል።ማሽኖቹ የተለያዬ ግልጋሎት የምሰጡና እጅግ ዘመናዊ ስሆኑ የዘርፉን ስራ የምያዘምኑ ናቸው።ገዋታ ሣይሌም 'ሽሺንዳና ቦንጋ ከተማ ላይ ያሉ 6 ኢንተርፕራይዞች ተጠቃሚ ሁነዋል።በዝህም በበጀት ዓመቱ የገቡት የማሽን አቅርቦት 30 ደርሷል ።ከዝህ ቀደም አንድ የማተሚያ ማሽን እና አንድ የዳቦ መጋገሪያ ማሽን የቀረበ መሆኑ ምታወስ ነው።

18/11/2023

በዞኑ ከ42 ሺህ በላይ ወጣቶችን የስራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነዉ:- አቶ ሚሊዮን ኃይሌ
***********************
ቦንጋ፦ህዳር 06/2016 ዓ.ም (የካፋ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በ2016 በጀት ዓመት ከ 42 ሺህ በላይ ስራ ፈላጊ ወጣቶችን ወደ ስራ ለማስገባት እየሰራ መሆኑን የካፋ ዞን ስራ፣ ክህሎት፣ እንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ መምሪያ አስታወቀ።

በየደረጃዉ የሚገኙ አካላት ለዕቅዱ መሳካት ኃላፊነታቸዉን በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባም መምሪያዉ ጥሪ አቅርቧል።

በጣቢያችን “ከቡና ጠጡ” ፕሮግራም ጋር ቆይታ ያደረጉት የመምሪያዉ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ኃይሌ፣ መምሪያዉ በገጠር የስራ ዕድል ፈጠራ፣ በከተማ ግብርናና በማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች ወጣቶችን በማደረጃት የስራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ ነዉ ብለዋል።

በተያዘዉ በጀት ዓመት በዞኑ ከ42 ሺህ በላይ ስራ ፈላጊ ወጣቶችን በመለየት የስራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን የጠቆሙት ኃላፊዉ፣ በሩብ ዓመቱ 14 ሺህ 731 ወጣቶችን ለመለየት ታቅዶ 9 ሺህ 626 ማከናወን መቻሉንም ተናግረዋል።

እንደ አቶ ሚሊዮን ገለፃ፣ ከእነዘህም ከ7 ሺህ 5 መቶ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች ቋሚ የስራ ዕድል ለመፍጠር የታደቀ ቢሆንም ተጠቃሚ ማድርግ የተቻለዉ 4 በመቶ ያህሉን ብቻ ነዉ።

በተለያዩ የስራ መስኮች የሚሰማሩ ወጣቶችን በሩብ ዓመቱ ከ3 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ለማስቆጠብ ታቅዶ ከ2 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ማስቆጠብ መቻሉንም ገልጸዋል።

በዞኑ በተለያዩ ጊዜያት ለስራ ዕድል ፈጠራ ተሰራጭቶ የመመለሻ ወቅቱ ከደረሰዉ ገንዘብ ዉስጥ ከ29 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ለማስመለስ የታቀደ ቢሆንም በእስካሁኑ ማስመለስ የተቻለዉ ከ2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ ብቻ እንደሆነም የመምሪያዉ ሀላፊ አቶ ሚሊዮን ሀይሌ ጠቁመዋል።

በዞኑ 36 የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎችን በመክፈት በተለያዩ እንተርፕራይዞች ለሚደራጁ ወጣቶች የተቀላጠፈ አገልግሎት በመሰጠት ላይ መሆኑንም ተናግረዋል።

አሁን እየተስተዋለ ያለዉን የኑሮ ዉድነት ለማቃለል በዞኑ በሚገኙ ከተሞች በከተማ ግብርና ለሚሰማሩ ወጣቶች ከ6 ሄክታር በላይ መሬት ለመለየት የታቀደ ቢሆንም ከቦንጋ፣ ጊንቦ፣ ደካና ሣይለም ከተሞች ዉጪ ሌሎች መዋቅሮች ምንም አለማዘጋጀታቸዉንም ጠቁመዋል።

ከዚም በተጨማሪ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተለያዩ ወጣቶችን በማሰማራት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የተናገሩት የመምሪያዉ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን፣ ወጣቶችን በማስቆጠብ ከልማት ባንክና ከደቡብ ካፒታል ጋር በማስተሳሰር የሊዝ ማሽን እንዲቀርብላቸዉ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

ለቆጠቡ ወጣቶች ብድር በወቅቱ አለመቅረብ፣ መሬት አለማዘጋጀት፣ ባለድርሻ አካላት ዘርፉን በባለበትነት አለመምራት፣ የክትትልና ድጋፍ ማነስና መሰል ችግሮች በዘርፉ የሚጠበቀዉ ዉጤት እንዳይመዘገብ ማነቆ እንደሆነም ተናግረዋል።

በቀጣይ እነዚህ ችግሮችን በመቅረፍ ስራ ፈላጊ ወጣቶችን ወደ ስራ ለማስገባት በየደረጃዉ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባም ኃለፊዉ ጥሪ አቅርበዋል።
ዘገባው ቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4 ነዉ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው ።

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፦
ፌስቡክ ገፃችንን
https://www.facebook.com/kfzgca
የቴሌግራም ቻናላችንን
https://t.me/ahkafaZGCAffairs ይወዳጁ ይከተሉ ይቀላቀሉ።

በካፋ ዞን ስራ ክህሎት ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ መምሪያ በማኑፋክቸሪንግ  ዘርፍ ከደቡብ ካፕታል በማሽን ሊዝ ቦንጋ ከተማ 2.8ሚሊዮን  ብር የማተሚያ ማሽን እና ገዋታ ወረዳ ቆንዳ ከተማ 1...
18/11/2023

በካፋ ዞን ስራ ክህሎት ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ መምሪያ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ከደቡብ ካፕታል በማሽን ሊዝ ቦንጋ ከተማ 2.8ሚሊዮን ብር የማተሚያ ማሽን እና ገዋታ ወረዳ ቆንዳ ከተማ 1.2 ሚሊዮን ብር የዳቦ መጋገሪያ ማሽን ሁለቱም ተገጥመው ስራ ጀምረዋልደ በቅርቡ 24 የጋርመንት ማሽኖች እና 8 የጣውላ መሰንጠቂያ ማሽኖችን ለማስገባት ከድርጅቱ ጋር ብርቱ ትግል በማድረግ ግዥ እየተፈፀመ ይገኛል።

አድማሱ አምቦ የግንባታ ዕቃዎች ማምረቻ ድርጅትበዴቻ ወረዳ ሞዲዮ ጎንበራ ቀበሌ የሚገኝ የተለያዩ ምርቶች ማለትም የተፈጨ አሸዋ፣ኮረት፣ብሎኬት እና ቴራዞ ማምረቻ፤በስሩ ለ50 ሰዎች በቋሚና ጊዜ...
16/09/2023

አድማሱ አምቦ የግንባታ ዕቃዎች ማምረቻ ድርጅት
በዴቻ ወረዳ ሞዲዮ ጎንበራ ቀበሌ የሚገኝ
የተለያዩ ምርቶች ማለትም የተፈጨ አሸዋ፣ኮረት፣ብሎኬት እና ቴራዞ ማምረቻ፤
በስሩ ለ50 ሰዎች በቋሚና ጊዜያዊ ስራ ዕድል የፈጠረ ድርጅት ሲሆን የተለያዩ የግንባታ ማሽነሪዎችን በማስመጣት በራሱ ሞያተኛ እያሰራ ያለና የሰለጠኑ ባለሙያዎች ያሉበት የኮንስትራክሽን ድርጅት ነው።
ድርጅቱ በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማራ ሲሆን በቅርቡም ከደቡብ ካፒታልና ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር በመቀናጀት ተጨማሪ ማሽነሪዎችን በማስመጣት ተጨማሪ የገበያ እና የስራ ዕድል ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል።
በማህበራዊ አገልግሎት ዘርፍ በአካባቢው የተቸገረውን በመርዳት ችግርተኛ ተማሪዎችን በማስተማር መሬት ላላቸው ዘር ገዝቶ በመስጠት ማህበራዊ ሀላፊነቱን በመወጣት ላይ ይገኛል።

ዴቻ ወረዳ ባጠራ ቀበሌ  በሰፈራ የገቡ ወጣቶች
15/09/2023

ዴቻ ወረዳ ባጠራ ቀበሌ በሰፈራ የገቡ ወጣቶች

15/09/2023
የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ኢንተርፕራይዝ እና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት በUIIDP ፕሮግራም የንግድ ሃሳብ ውድድር ተደረገቦንጋ ፣ ግንቦት 17 ቀን 2015 ዓ.ም የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ኢንተ...
25/05/2023

የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ኢንተርፕራይዝ እና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት በUIIDP ፕሮግራም የንግድ ሃሳብ ውድድር ተደረገ

ቦንጋ ፣ ግንቦት 17 ቀን 2015 ዓ.ም

የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ኢንተርፕራይዝ እና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት በUIIDP ፕሮግራም የንግድ ሃሳብ ውድድር ተደርጓል።

በውድድሩ ላይ አምስት የንግድ ሃሳብ ለውድድር የቀረበ ሲሆን ከተለያዩ ተቋማት ባለድርሻ አካላት የተገኙ ማለትም ከቦንጋ ዩኒቨርሲቲ እና ከቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እንዲሁም ከከተማ አስተዳደሩ የስነም ግባር ጽ/ቤት ሀላፊ እና ከጽህፈት ቤቱ የተውጣጡ ባለሙያዎች እና አመራሩ በተገኙበት ውድድሩ ተደረጓል።

በውድድሩም ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ አሸናፊ የተለየ ሲሆን ለአሸናፊዎችም የገንዘብ እና የሰርቲፍኬት ሽልማት ተበርክቷል።

የጽ/ቤቱ ምክትል ሀላፊ አቶ ሔኖክ ወ/ገብረኤል ውድድሩን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት ውድድሩ አሸናፊን መለየት ግዴታ ስለሆነ እንጂ በሁሉም ተወዳዳሪ የቀረበው ሀሳብ የሚደገፍ መሆኑን ጠቁመው ሁሉም ተወዳዳሪዎች ጠንክረው በመስራት ሃሳባችውን ከግቢ ማድረስ ይጠበቅባቿል ብሏል።
ዘገባው፡የቦንጋ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ነው!

ዴቻ ወረዳ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት የወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ ተደራጅተው ብድር ለጠየቁ 34 ኢንተርፕራይዝ ማህበራት የ4ሚልዬን 60 ሽህ ብ...
24/05/2023

ዴቻ ወረዳ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት የወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ ተደራጅተው ብድር ለጠየቁ 34 ኢንተርፕራይዝ ማህበራት የ4ሚልዬን 60 ሽህ ብር ብድር አፀደቀ:

ቦንጋ_ግንቦት_16_2015_ዓ/ም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዴቻ ወረዳ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት የወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ ተደራጅተው ብድር ለጠየቁ 34 ኢንተርፕራይዝ ማህበራት የ4ሚልዬን 60 ሽህ ብር ብድር አፀደቀ:

የዴቻ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ወንዱ አደመ እንዳሉት ወጣቱ በዘላቅነት ተጠቃሚ ለመሆን የምወስዱትን ብድር ባቀረቡት ቢዚነስ ፕላናቸውን መሠረት መሥራት እንዳለባቸውና መንግስት እየፈጠረ ያለውን ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም ሀገሪቱ ለምታልመው ወጣቱን ላሳተፈ ሁለንተናዊ ብልጽግና የራሳቸውን ድርሻ በኢኮኖሚው ዘርፍ እንድወጡ ጥሪያቸውን አቀርበዋል።

በተያያዘ የስራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤት ኮሚቴዎች እንዳሉት ወጣቱ በምፈጠርለት ስራ ውጤታማ ለመሆን በቁርጠኝነት ለስራቸውና ለግዜያቸው ታማኝ በመሆን መሥራት አለባቸው ብለዋል።

የዴቻ ወረዳ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እንዳሌ ከበደ አክለው የወረዳው ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት ባለፉት 10 ወራት ለ32 ማህበራት 3ሚልዬን170ሽህ ብር ብድር አገልግሎት እንደሰጠ አስታውሰዋል።

በዛሬው ዕለት የ4ሚልዬን 60 ሽህ ብር ብድር ለመስጠት የተደራጁ ኢንተርፕራይዝ ማህበራት ያቀረቡትን ፕሮፖዛል ኮሚተው ገምግመው ማጽደቁን ኃላፊው ገልጿል።

ኃላፊው አክለው የተደራጁ ወጣቶች በዕርባታ፣በሬ በማደለብ፣ በግ በማሞከት፣ በእንጨትና ብረታብረት ስራ እንድሁም በስፌት ስራ መደራጀታቸውን ገልጿል።

በመጨረሻም ኃላፊው እንዳሉት ቀጣይ የስራ ዕድል ፈጠራ ምክር ቤቱ እስከታች ወርዶ ተበዳሪ ወጣቶች ያሉቤትን ደረጃ በመጎብኘት እንደምያጠናክሩ ገልፀው በቀሪ ወራት በብድር አመላለስ ሞዴል ኢንተርፕራይዝ ማህበራት ልየታ ሥራን በተመረጡ ክላስተሮች እንደሚሰራና ለወጣቱ ፊህታዊ ተጠቃሚነት እርብእርብ እንደሚደረግ አሳስበዋል።
ሲል የዘገበው የዴቻ ወረዳ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው

የካፋ ዞን ኢንተርፕራይዞችና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ ሀላፊ የነበሩት ወ/ሮ እታገኝ ወልዴ  ከሚመሩበት ሰክተር በሌላ ሹመት የካፋ ዞን ክህሎትና ቴክኖሎጂ መምሪያ ሀላፊ በመሆን ሀላፊነት በመሰ...
27/04/2023

የካፋ ዞን ኢንተርፕራይዞችና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ ሀላፊ የነበሩት ወ/ሮ እታገኝ ወልዴ ከሚመሩበት ሰክተር በሌላ ሹመት የካፋ ዞን ክህሎትና ቴክኖሎጂ መምሪያ ሀላፊ በመሆን ሀላፊነት በመሰጠቱና በምትካቸው የቀድሞ የካፋ ዞን ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ሀላፊ የነበሩት አቶ ሚሊዮን ሀይሌ ሀላፊነት በመሰጠቱ ሁለቱ አመራሮች ከሰክተሩ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በተሰሩ ስራዎችና በቀሪ ስራዎች ዙሪያ የውይይት፣ የሽኚትና የትውውቅ መድረክ ተካሂዷል፡፡
በዚህም የካፋ ዞን ኢንተርፕራይዞችና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ ማኔጅመንትና የሰክተሩ ባለሙያ ለነበረው ቆይታ የቀድሞ የመምሪያውን ሀላፊ እያመሰገነ በሄዱበት መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቸው ፤አዲስ ለመጡት የመምሪያ ሀላፊ ቆይታቸው ያማረ እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን፡፡

Address

Bonga

Telephone

+251904861163

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kaffa Zone Work,Technique , Enterprise & Industry Dev't Dep't posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share