28/03/2023
የደቡብ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ሥራ አመራር ቦርድ የተለያየ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት ውሳኔ አሳለፈ።
***
የድርጅቱ ሥራ አመራር ቦርድ በአዲስ አበባ ከተማ ተሰብስቦ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቷል።
ቦርዱ የ2015 በጀት ዓመት የተከለሰ ዕቅድና የስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ውባየሁ ትዕዛዙ በኩል ቀርቦ አድምጧል።
ዋና ሥራ አስኪያጁ ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ በተከለሰ ዕቅድ 409 ፕሮጀክቶችን በመስራት 243,387,560 ብር ለመሰብሰብ አቅዶ ወደሥራ መግባቱን በሪፖርቱ አመላክቷል።
ድርጅቱ በስድስት ወራት 223 ፕሮጀክቶችን በመከወን 80,918,091 ብር በመሰብሰብ 65.6% መፈጸም መቻሉን ሥራ አስኪያጁ አክለዋል።
በመቀጠልም የ2014 በጀት ዓመት የውጪ ኦዲት ሪፖርት ቀርቦ አድምጧል።
ቦርዱ ከቀረቡለት ሪፖርቶች እያደገ የመጣ አፈጻጸም መመልከቱን ገልጾ ለዚህም የተቋሙ አመራር እና ሠራተኛ ዕውቅና ልሰጠው ይገባል ሲል አድናቆቱን ገልጿል።
የሥራ አመራር ቦርዱ ሰብሳቢ የሆኑት የተከበሩ ዓለማየሁ ባውዲ፣ የድርጅቱን የማስፈጸም አቅም መገንባት ወሳኝ መሆኑን እንዲሁም ያሉትን ዕድሎች ሁሉ አሟጦ መጠቀም እንደሚገባ አንስተዋል።
አክለውም ድርጅቱ አዳዲስ ክልሎች እኩል ትኩረት በመስጠት፤ በአስተዳደራዊ ወሰን ሳይታጠር ህብረተሰቡን ማዕከል አድርጎ ያለልዩነት እንዲያገለግል አሳስበዋል።
በቀረበው የውጪ የኦዲት ሪፖርት መነሻም በህብረት ስምምነቱ ላይ በተቀመጠው አሰራር መሠረት ለድርጅቱ ሠራተኞች የአንድ ወር ደመወዝና አንድ ከግማሽ ቦነስ እንዲከፈል ይሁንታ ሰቷል።
ሌሎች የተዘጋጁ የሰው ሃይል፣ የግዥ፣ የንብረት እና የበጀት አስተዳደር መመሪያዎችን በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ድጋሚ በመሰብሰብ ውሳኔ ለማሳለፍ ቀነ ቀጠሮ በመያዝ ተለያይቷል።